• Home
  • About Us
    • Our Mission and Vision
    • Objectives
    • History
    • Board of Directorss
    • Message From CEO
    • Our Leadership Team
  • Investment
  • Portfolio
    • Transport and Logistics
    • Energy and Connectivity
    • Financial Services
    • Mining, Engineering and Chemicals
    • Hospitality
    • Agriculture and Processing
    • Manufacturing
    • Trading
    • Construction and Real estate
  • Resources
    • Audit Report
    • Annual Report
    • Publications
    • Laws and Regulations
  • More
    • News and Media
    • Gallery
    • Career
    • Contact Us
qt=q_95

አሊኮ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ ፕሮጀክቶቻቸው ላይ የሚያደርጉትን ማስፋፊያና አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች አስታወቁ

  • February 15, 2025
  • admin
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ - የካቲት 08፣ 2017– ዳንጎቴ ግሩፕ የተሰኘው የአፍሪካ ግንባር ቀደም ኢንዱስትሪያል ኩባንያ እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በጋራ በመሆን በዛሬው እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ ያሉት ፕሮጀክቶቹ ላይ እያከናወነ ያለውን ከፍተኛ የማስፋፊያ ስራ አሳውቀዋል። ይህም የሀገሪቱ መስህብ በአፍሪካ ቀዳሚ...

አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ – የካቲት 08፣ 2017– ዳንጎቴ ግሩፕ የተሰኘው የአፍሪካ ግንባር ቀደም ኢንዱስትሪያል ኩባንያ እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በጋራ በመሆን በዛሬው እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ ያሉት ፕሮጀክቶቹ ላይ እያከናወነ ያለውን ከፍተኛ የማስፋፊያ ስራ አሳውቀዋል። ይህም የሀገሪቱ መስህብ በአፍሪካ ቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ መሆኗን ማሳያ ሆኗል።

የዳንጎቴ ግሩፕ ሊቀመንበር እና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሊኮ ዳንጎቴ ስለ አዲሱ ኢንቨስትመንት አቅጣጫቸው ሲናገሩ፡ “ሁሌም በኢትዮጵያ በሚኖረኝ ጉብኝት ደስተኛ ነኝ። በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባደረግኩት ጉብኝትና ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ባደረግሁት ውይይት፣ በሀገሪቱ እየታዩ ያሉ ለውጦችን ሳይ ለተጨማሪ ኢንቨስትመንት ተነሳስቻለሁ። በሙገር የሚገኘው 2.5 ሚሊዮን ቶን ሲሚንቶ ፋብሪካችን ከፕሮጀክቶቻችን አንዱ እና ዋነኛው ነው። ውጣ ውረዶች ቢያጋጥመንም በዚህ ኢንቨስትመንት በጣም ደስተኛ ነኝ” በማለት “100% ብድር እና 100% የትርፍ ድርሻን በተሳካ ሁኔታ ወደ ሀገር ቤት መመለሳችንን በደስታ እገልጻለሁ” ሲሉ አክለው ተናግረዋል።

አቶ ዳንጎቴ በአፍሪካ ውስጥ ካሉት ትላልቅ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነውን ‘የዳንጎቴ ማጣሪያ’ በተሳካ ሁኔታ ሥራ ካስጀመሩ በኋላ ትልልቅ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን ለማቆም አቅደው ነበር። ሆኖም የኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ሁኔታ እየተሻሻለ መምጣቱ እና ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር መገናኘታቸው አመለከታቸውን እንደለወጠው ገልጸዋል። በመሆኑም ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ያለውን የሲሚንቶ የማምረት አቅሙን በእጥፍ ለማሳደግ ዝግጁነቱን አረጋግጧል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ በበኩላቸው የማስፋፊያ ስራውን በደስታ መቀበላቸውን ተናግረው ኢትዮጵያ የግሉ ዘርፍ እድገትን ለማሳደግ ያላትን ቁርጠኝነት ሲገልፁ “ኢትዮጵያ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለኢንቨስትመንት እና ለስራ እድል ፈጠራ ቅድሚያ የሚሰጥ የኢኮኖሚ ለውጥ እያስመዘገበች ነው። ይህን ተከትሎ ዳንጎቴ ግሩፕ በአገራችን አሻራውን ሲያሰፋ በማየታችን ተደስተናል። ይህ ኢንቨስትመንት በኢትዮጵያ የንግድ አካባቢ ላይ የመተማመን ምልክት ሲሆን ለመሰረተ ልማት እና ለኢኮኖሚ እድገታችን ከፍተኛ አስተዋፅዖ ይኖረዋል” ብለዋል።

በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ከተነሱ ቁልፍ ነጥቦች መካከል

● ሙገር የሚገኘውን የዳንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ አዲሱ ማስፋፊያ የፋብሪካውን የማምረት አቅም በአመት ወደ 5 ሚሊዮን ቶን ይጨምራል።

● ዳንጎቴ ግሩፕ በናይጄሪያ 60,000 ሄክታር መሬት ላይ የሚሸፍነውን የስኳር ልማት ልምዱን በመከተል በኢትዮጵያ የስኳር ኢንዱስትሪ ውስጥ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን ለማስፈር በኢትዮጵያ ያለውን የኦሞ ኩራዝ ስኳር ኩባንያ ያስፋፋል።

● የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚረዳው የሀገሪቱ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ከተፈጠረ በኋላ በኢትዮጵያ የዩሪያ ማምረቻ ፋብሪካን ለመትከል ታስቧል።

አቶ ዳንጎቴ የአህጉሪቱን እድገት ለመምራት ‘የአፍሪካ የንግድ መሪዎች’ ያላቸው ሚና ላይ አፅንዖት ሰጥተዋል፡ “አፍሪካ የምትለማው በአፍሪካውያን ነው። የፖለቲካ መሪዎቻችን የአፍሪካ ህብረትን ለማጠናከር በሚሰሩበት ወቅት፣ እኛ ደግም የንግድ መሪዎች እንደመሆናችን መጠን በአህጉሪቱ ያለውን የንግድ ትስስራችንን በማጠናከር ጥረታቸውን መደገፍ አለብን” ብለዋል።

እነዚህ ኢንቨስትመንቶች የዳንጎቴ ግሩፕን በአፍሪካ ቀዳሚ ሲሚንቶ የማምረት አጠቃላይ አቅሙን በዓመት ወደ 55 ሚሊዮን ቶን ያሳድጋል። በኢትዮጵያ የስኳር እና ማዳበሪያ ኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ተፅእኖ ይኖረዋል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን ይህም የስራ እድል ፈጠራን፣ የግብርና ምርታማነትን እና የኢንዱስትሪ ልማትን ይደግፋል።

Share:

More Posts

Ethiopian Investment Holdings Celebrates Revenue Jump

EIH paid 98 bln in taxes over nine monthsEthiopian Investment Holdings (EIH) reported revenues of 1.5 trillion birr over the first three quarters of the

Ethiopia’s Sovereign Wealth Fund Ranked Largest in Africa

Ethiopian Investment Holdings (EIH) was ranked as the 34th biggest sovereign wealth fund in the world, with nearly 45 billion dollars of assets. The Sovereign Wealth Fund Institute’s (SWFI) latest ranking places EIH as …

EIH terminates Battery-Swap Partnership with Dodai Group

Ethiopian Investment Holdings (EIH), the state-owned sovereign wealth fund overseeing 40 enterprises, has ended its partnership with Japan’s Dodai Group Inc. to deploy battery-swapping stations for electric motorcycles….

EIH Terminates MoU with Dodai for Battery Swap Stations Network

Ethiopian Investment Holdings (EIH) announced the termination of its partnership agreement with electric mobility startup Dodai Group Plc five months after the two sides agreed to establish a network of battery swap sta…

PrevPreviousPress Release: EIH and AIH Sign Memorandum of Understanding
NextEIH, EABC & Asset Green sign a Shareholders AgreementNext

Ethiopian Investment Holdings

Quick Links

  • Home
  • About Us
  • Investment
  • Portfolio
  • Contact Us

Contact

+251(0)111 70 45 40

info@eih.et

General Winget St, Hilcoe Building 5th floor, Addis Ababa ,Ethiopia

Copyright © 2025 All Right Reserved